አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው የአርሰናል የቀድሞ ተጫዋች ሳንቲ ካዞርላ ራሱን ከእግር ኳስ ዓለም ማግለሉን ይፋ አድርጓል፡፡
የመድፈኞቹ የቀድሞ ተጫዋች ሳንቲ ካዞርላ በ41 ዓመቱ ጫማውን መስቀሉን በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡
ተጫዋቹ ያለፉትን ሦስት የውድድር ዓመታት በልጅነት ክለቡ ሪያል ኦቬዶ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡
ሳንቲ ካዞርላ በተጨዋችነት ዘመኑ ለአርሰናል፣ ቪያሪያል፣ ማላጋ እና አል ሳድ ለመሳሰሉ ክለቦች ተጫውቶ አሳልፏል፡፡