29 January 2019, Ethiopia, Addis Abeba: A young woman works wood at the Federal Technical and Vocational Education and Training Institute (TVET). Photo: Britta Pedersen/dpa-Zentralbild/dpa (Photo by Britta Pedersen/picture alliance via Getty Images)

የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተማሪዎች 12ኛ ክፍልን ሲጨርሱ የሙያ ባለቤት ይሆናሉ – ትምህርት ሚኒስቴር

By Tibebu Kebede

August 31, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲሱ ስርዓተ-ትምህርት ተማሪዎች 12ኛ ክፍልን ሲጨርሱ የሙያ ባለቤት እንደሚሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ በአጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ውስጥ የሙያ ትምህርቶችን በሁሉም የሙያ ዘርፎች በመስጠት የተማረ እና በዘርፉ እውቀት ያለው ባለሙያ እንዲፈጠር ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን ብለዋል።