አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሊባኖስ በአሰሪዎች በደልና የመብት ጥሰቶች፣ የአካልና የስነ-ልቦና ጉዳት የደረሰባቸው እንዲሁም መጠለያና ምግብ ያጡ የነበሩ 165 ኢትዮጵያውያን ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ።
ሊባኖስ የሚገኘው ቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤት ከኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ማህበር እና ከሌሎች ድጋፍ ከሚያደርጉ በጎ አድራጎት ድርጅቶችን ግለሰቦች ጋር በመተባበር የጉዞ ሰነዶቻቸውንና ሌሎች ጉዳዮችን በመጨረስ ትናንት ማታ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ተደርጓል ተብሏል።