አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሲሼልስ ፕሬዚዳንት ፓትሪክ ሄርሚኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልጽግና ፓርቲ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በማሸነፋቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በመልዕክታቸው የምርጫው ውጤት የኢትዮጵያ ሕዝብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) አስተዳደር ላይ ያለውን ጠንካራ እምነት የሚያመላክት ነው ብለዋል፡፡
ሲሼልስ እና ኢትዮጵያ በመከባበርና በትብብር ላይ የተመሰረተ የረዥም ዓመታት ግንኙነት እንዳላቸው አውስተዋል፡፡