አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ ምሽት ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) እና ከባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገናል ብለዋል።
በውይይቱ በአጋርነት፣ ዕድገት እና በአፍሪካ የወደፊት ዕድሎች ዙሪያ መምከራቸውን ጠቁመዋል።