የሀገር ውስጥ ዜና

የአማራ ክልል ምክር ቤት 12ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ

By abel neway

July 30, 2026

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤውን በባህርዳር ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።

በጉባኤው የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም ልዩ ልዩ አዋጆች እና የ2019 የክልሉ በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቦ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል ሲል አሚኮ ዘግቧል።