አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሊባኖስ 18 በእስር ላይ የነበሩ ሰዎችን ጨምሮ 90 ኢትዮጵያውያን መመለሳቸውን ሊባኖስ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤቱ በሊባኖስ 2 እስር ቤቶች ታስረው የነበሩ 19 ኢትዮጵያውያንን ከፍርድ ቤቶችና እስር ቤቶቹ ጋር በመነጋገርና በማስፈታት፤ ከእነዚህም 18 ሰዎች የመውጫ ቪዛ ተሰርቶላቸው ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ማድረጉን አስታውቋል።