የሀገር ውስጥ ዜና

በሊባኖስ 18 በእስር ላይ የነበሩ ሰዎችን ጨምሮ 90 ኢትዮጵያውያን ተመለሱ

By Feven Bishaw

September 01, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሊባኖስ 18 በእስር ላይ የነበሩ ሰዎችን ጨምሮ 90 ኢትዮጵያውያን መመለሳቸውን ሊባኖስ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

ቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤቱ በሊባኖስ 2 እስር ቤቶች ታስረው የነበሩ 19 ኢትዮጵያውያንን ከፍርድ ቤቶችና እስር ቤቶቹ ጋር በመነጋገርና በማስፈታት፤ ከእነዚህም 18 ሰዎች የመውጫ ቪዛ ተሰርቶላቸው ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ማድረጉን አስታውቋል።