ዓለምአቀፋዊ ዜና

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሊባኖስ አዲስ መንግስት እንድትመሰርት ጠየቁ

By Meseret Demissu

September 01, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 26 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሊባኖስ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር መሾሙን ተከትሎ ሀገሪቱ በፍጥነት አዲስ መንግስት እንድትመሰርት ጠይቀዋል።

አዲሱን የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ የያዙት በጀርመን የሊባኖስ አምባሳደር የነበሩት ሙስጠፋ አዲብ መሆናቸውም ተነግሯል። ይህንን ተከትሎም ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ሀገሪቱ በፍጥነት አዲስ መንግስት እንድትመሰርት ጠይቀዋል።