አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን የባምባሲ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ በክልሉ ቀደም ሲል ወደ ሥራ ከገቡት የቤጉ-መሶብ እና አሶሳ መሶብ አንድ ማዕከላት በተጨማሪ ሦስተኛው ማዕከል ሆኖ ሥራ ጀምሯል። በክልሉ አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በተለያዩ ከተሞች የማስፋት ሥራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል፡፡