የሀገር ውስጥ ዜና

የሀገራዊ ምክክር ም/ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገ/ሥላሴ የሀገራዊ ምክክሩን አሁናዊ ሁኔታ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

By betelhem girma

August 13, 2026

👉 የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ሒደት ሥራዎች በእቅዳችን መሰረት በሚገባ እየተካሄዱ ነው፡፡

👉 እያንዳንዳቸው 500 አባላት ያሏቸው ስምንቱም ቡድኖች ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

👉 በሒደቱ ውስጥ አለመግባባቶች አልነበሩም ማለት አይቻልም፤ እነዚህ አለመግባባቶችና ግጭቶች ምክክሩ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ይበልጥ የተረዳንባቸው ናቸው ፡፡

👉 ተመካካሪዎቹ እነዚህን አለመግባባቶችና ግጭቶች በመደማመጥ መፍታት ችለዋል፡፡

👉 በ500 ተሳታፊ የተቋቋሙት ቡድኖች በቡድን ሲመካከሩ ቆይተው አብዛኞቹ መግባት ላይ የደረሱባቸውን ምክረ ሃሳቦች አጽድቀው አስረክበዋል፡፡

👉 ተመካካሪዎቹ በአብዛኞቹ ጉዳዮች ላይ ተስማምተው ሥራቸውን እያጠናቀቁ ነው፡፡

👉 በምክክር ጉባዔው በስምንቱ ቡድኖች ጸድቀው የሚቀርቡ ምክረ ሀሳቦችን የሚያጣጥም፣ ድግግሞሽ ያለባቸውን ሀሳቦች ወደ አንድ የሚያመጣ ቡድን ዛሬ ስራውን ይጀምራል፡፡

👉 እያንዳንዳቸው 500 አባላት ያሏቸው ስምንቱም ቡድኖች ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህም አጠቃለን ለምናቀርባቸው ሀሳቦች ያግዘናል፡፡

👉 ምክክር ጉባዔው ሒደት ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችን እየተቀበልን ነው፤ እየመረመርን ውሳኔ እየሰጠን እንሄዳለን፡፡

👉 በአሁኑ ሰዓት 3/4ኛ የሚሆነው ሥራችን እየተጠናቀቀ ነው፤ ቀጣዩ ሥራችን የሚሆነው ለህዝብ ይፋ የማድረግ ሒደት ነው፡፡

በቤተልሔም ግርማ