የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያና ጀርመን የኢነርጂ አጋርነት የፈጠራ ውድድር ፕሮግራም ይፋ ሆነ

By Meseret Demissu

September 02, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 27 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ጀርመን የኢነርጂ አጋርነት ፕሮግራም በኢነርጂ ዘርፍ የፈጠራ ውድድር ይፋ መሆኑን የዉኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የፈጠራ ውድድሩ ይፋ የሆነው ከ90 በላይ የኢትዮጵያና የጀርመን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ተወካዮች፣ የግል ዘርፍ ተሳታፊዎች እና በፈጠራ ዘርፍ ያሉ ባለሙያዎች በተሳተፉበት በበይነ መረብ በተካሄደበት ወቅት መሆኑ ተገልጿል።