የሀገር ውስጥ ዜና

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

By emebet sisay

August 24, 2026

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል (መውሊድ) የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ከንቲባዋ በመልዕክታቸው፥ በዓሉን እንደከዚህ ቀደሙ የተቸገሩትን በመርዳት፣ ለሌላቸው በማካፈልና የታረዙትን በማልበስ እንዲሁም የታመሙትን በመጠየቅ እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል።