አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦልማ) ልዩ አዳሪ ት/ቤት ተማሪ የሆነው ጃላል ግርማ ኩሳ በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና 591 ነጥብ 6 በማምጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል፡፡
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 አጠቃላይ ውጤት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው በአዳማ የሚገኘው የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦልማ) ልዩ አዳሪ ት/ቤት ተማሪ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
በዚህ መሰረትም ተማሪ ጃላል ግርማ በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ 591 ነጥብ 6 ውጤት በማምጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛውን ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን የኦሮሚያ ልማት ማህበር ዋና ዳይሬክተር ደጀኔ ኢቲቻ ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል፡