አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፋና ላምሮት በምዕራፍ 23 ከምድብ ሁለት 6 ተወዳዳሪዎች ጋር በነገው ዕለት ቅዳሜ ቀጥሎ ይካሄዳል።
በነገው ውድድር የምድብ ሁለት ተወዳዳሪዎች ከዛየን ባንድ ጋር በሁለት ዙር ውድድራቸውን ያቀርባሉ።
በምዕራፉ ፍፃሜ የሚቀሩ አራት ተወዳዳሪዎች የ1 ሚሊየን ብር ሽልማት ተዘጋጅቶላቸዋል።
ነገ ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደውን ውድድር 6 ሰዓት ላይ በሁለቱም የፋና ቴሌቭዥኖችና በሁሉም የፋና ዲጂታል አማራጮች በቀጥታ ስርጭት ይከታተሉ።