አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 28 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የኮቪድ 19 ወረርሽኝ 47 ሚሊየን የሚሆኑ ተጨማሪ ሴቶችን እና ልጃገረዶችን ወደ ድህነት ሊያስገባ እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስጠነቀቀ።
ሴቶች በአብዛኛው መደበኛ ባልሆነ ኢኮኖሚ ውስጥ የመሥራት ዕድላቸው ሰፊ ከመሆኑም ባለፈ በወረርሽኙ በጣም በተጎዱና ለረዥም ጊዜ በተዘጉ ዘርፎች ላይ በመሰማራታቸው ከወንዶች በበለጠ በፍጥነት ሥራቸውን ማጣታቸው ተገልጿል።