አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ የስኳር እጥረት እንዳይከሰት 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ተገዝቶ ወደ ሀገር ውስጥ እየገባ መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚኖረውን ከፍተኛ የስኳር ፍላጎት ለማሟላትና የአቅርቦት እጥረት እንዳይገጥም 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ግዥ ተፈጽሞ ወደ ሀገር ውስጥ በመግባት ላይ መሆኑን በሚኒስቴሩ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ ገልፀዋል።