የሀገር ውስጥ ዜና

ባለፈው አንድ ሳምንት ከ40 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ

By Tibebu Kebede

September 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ግምታዊ ዋጋቸው ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የሆኑ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ከነሐሴ 21 እስከ 28 ቀን 2012 ዓ.ም ባሉት ቀናት በተለያዩ የጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢዎች መያዛቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።

በተጨማሪም በብሔራዊ ባንክ ፍቃደ ያላገኘ 2000 የአሜሪካን ዶላር በመንገደኛ እጅ ተገኝቶ የተወረሰ መሆኑ ነው የተገለፀው፡፡