የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ በጎርፍ ምክንያት ለተፈናቀሉ ከ177 ሺህ በላይ ዜጎች የሰብአዊ እርዳታ የመስጠት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

By Tibebu Kebede

September 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ በጎርፍ ምክንያት ለተፈናቀሉ ከ177 ሺህ በላይ ዜጎችን የሰብአዊ እርዳታ የመስጠት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የብሄራዊ የአደጋ ስጋትና አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።

ኮሚሽኑ ለፋና ብሮካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፀውበክረምቱ ከመደበኛ በላይ የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የጎርፍ አደጋ እስከ አሁን በሰባት ክልሎች ጉዳት አድርሷል።