አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አመራሮችና ሠራተኞች የገበታ ለሃገር የልማት ጥሪ በመቀበል 102 ሚሊየን ብር የሚሆን የአንድ ወር ደሞዛቸውን ድጋፍ አደረጉ፡፡
መንግሰት ከዚህ በፊት በገበታ ለሸገር ያቀረበውን የልማት ጥሪ በመቀበልና ፈጣን ምላሽ በመስጠት በአጭር ጊዜ ውስጥ አንድነት ፓርክ፣ ሸገር የወንዝ ዳርቻ መናፈሻ፣ እንጦጦ ፓርክ ፍፁም በማይታመን መልኩ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጥራቱን ጠብቆ በከፍተኛ ርብርብ ውጤቱን ማየት ተችሏል ብሏል አገልግሎቱ፡፡