የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ያመጠቀቻት ሳተላይት ምድርን መቃኘት ጀመረች

By Tibebu Kebede

December 20, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ያመጠቀቻት ሳተላይት ምድርን መቃኘት መጀመሯን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ምድርን እየቃኘች እና በፎቶ እየመዘገበች መረጃ የምትሰበስበው “ETRSS-1” በዛሬው ዕለት ነበር ወደ ህዋ የመጠቀችው።