አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በብልፅግና ፓርቲ አመራር ዘንድ ያለው ዝግጁነት ተስፋ ሰጪ ነው አሉ የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባልና የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ።
የብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለአንድ ሳምንት በአዳማ ከተማ ሲሰጥ የቆየውን የአመራር ስልጠና ዛሬ ማጠናቀቁን የክልሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።