አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከመላው ማህበረሰብ ጋር በመቀናጀት በ2013 ዓ.ም የተጠናከረ የወንጀል መከላከል ስራ እንደሚሰራ ገልጿል።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፈንታ÷ የሀገሪቱን ሰላምና ደህንት ለማስከበር በተለያዩ አካባቢዎች ተሰማርተው ላሉ የፖሊስ አመራሮችና አባላት እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን አደረሳቹ መልእክት አስተላልፈዋል።