የሀገር ውስጥ ዜና

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከህዝብ ጋር በመቀናጀት በአዲሱ ዓመት የተጠናከረ የወንጀል መከላከል ስራ እንደሚሰራ ገለፀ

By Meseret Demissu

September 07, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከመላው ማህበረሰብ ጋር በመቀናጀት በ2013 ዓ.ም የተጠናከረ የወንጀል መከላከል ስራ እንደሚሰራ ገልጿል።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፈንታ÷ የሀገሪቱን ሰላምና ደህንት ለማስከበር በተለያዩ አካባቢዎች ተሰማርተው ላሉ የፖሊስ አመራሮችና አባላት እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን አደረሳቹ መልእክት አስተላልፈዋል።