አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቶ ጃዋር መሃመድና በቀለ ገርባን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ እስከ መስከረም 8 2013 ዓ.ም ክስ እንዲመሰርት ብይን ሰጠ።
ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋር መሃመድና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ ከጳጉሜን 2 እስከ ጳጉሜን 5 2012 ዓ.ም የተሰሙ የምስክር ቃል ተገልብጦ ወስዶ እስከ መስከረም 8 ቀን 2013 ዓ.ም ክስ አንዲመሰርት ነው ብይን የሰጠው።