አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ልዩ መልእክተኛ እና የኢፌዴሪ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ጋር ተወያዩ።
በደቡብ ሱዳን ጁባ በተካሄደው ውይይትም የሁለቱን ሀገራት ፍላጎት በሚያሟላ መልኩ መንገድና ኤሌክትሪክን ጨምሮ ሀገራቱ በጥምረት በሚሰሯቸው ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ዙሪያ ተወያይተዋል።