አዲስ አበባ ፣ጳጉሜን 3 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) “ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን እንደርሳለን” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጅው ሀገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ፕሮግራም ዛሬ የቁጥጥር ቀን ሆኖ ተከብሮ ውሏል፡፡
የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ዕለቱን በማስመልከት እንዳሉትም የቁጥጥር ሥርዓቱን በማጠናከር፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ በትራፊክ አደጋ የሚደርሰውን የሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት በጋራ መከላከል አለብን።