የሀገር ውስጥ ዜና

በሀገር አቀፍ ደረጃ ህግን ለማስከበር በተደረገው የክትትልና የቁጥጥር ስራ 141 ሺህ 369 አጥፊ አሽከርካሪዎች ተቀጡ

By Feven Bishaw

September 08, 2020

አዲስ አበባ ፣ጳጉሜን 3 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) “ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን እንደርሳለን” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጅው ሀገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ፕሮግራም ዛሬ የቁጥጥር ቀን ሆኖ ተከብሮ ውሏል፡፡

የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ዕለቱን በማስመልከት እንዳሉትም የቁጥጥር ሥርዓቱን በማጠናከር፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ በትራፊክ አደጋ የሚደርሰውን የሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት በጋራ መከላከል አለብን።