የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ከ60 ሺህ አለፈ

By Tibebu Kebede

September 08, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 60 ሺህ 784 መድረሱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 14 ሺህ 815 የላብራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 136 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።