አዲስ አበባ ፣ዻጉሜ 5 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለፀጥታ ሲባል በአዲስ አበባ ማንኛውም ግለሰብ ርችት መተኮስ እንደማይችል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት የሚዲያ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በሰጡት መግለጫ÷ ርችትን ምክንያት በማድረግ የሽብር ጥቃት ለማድረስ እየተዘጋጁ ያሉ ግለሰቦች መኖራቸውን ፖሊስ በጥናት ደርሶበታል ብለዋል።