ዓለምአቀፋዊ ዜና

ከወር በፊት ፍንዳታ በተከሰተባት የቤሩት ከተማ እሳት መነሳቱ ተገለጸ

By Meseret Demissu

September 10, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ ) ከወር በፊት ፍንዳታ በተከሰተባትና ከ190 በላይ ሰዎች ለህልፈት በተዳረጉባት የቤሩት የወደብ ከተማ እሳት ተነስቷል።

እሳቱ የተነሳው በከተማዋ የነዳጅና የጎማ እቃ ቤት ላይ ሲሆን÷ በዚህም በከተማዋ የእሳቱ ጭስ ወደ ሰማይ ሲወጣ መታየቱ ተገልጿል።