አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአውስትራሊያና ኒውዝላንድ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን 233 ሺህ 557 የአሜሪካ ዶላር በስጦታና በቦንድ ግዥ ፈፀሙ።
“ግድቡ እንዲጠናቀቅ የበኩሌን አስተዋፅዖ አደርጋለሁ፤ ለትውልድ አሻራዬን አስቀምጣለሁ” በሚል መሪ ቃል ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጄክት ማስፈጸሚያ የሚውል የገንዘብ አስተዋፅዖ ለማበርከት በሀገራቱ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የታደሙበት የቪዲዮ ኮንፈረንስ ተካሂዷል።