አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያን እና ትውልደ ኢትዮጵያን ወደ ኤምባሲ መምጣት ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ሆነው ፖስፖርት እና የትውልድ ኢትዮጵያን መታወቂያ (Origin ID) ማሳደስና መረከብ የሚችሉበት ስርአት በመዘርጋት ተግባራዊ ማድረግ ተጀመረ።
ስርዓቱን የኢሚግሬሽን ዜግነት እና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና ቪዲቸር ከተባለ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ጋር በመተባበር ነው ተግባራዊ ማድረግ የጀመረው።