Law and Justice concept. Mallet of the judge, books, scales of justice. Gray stone background, reflections on the floor, place for typography. Courtroom theme.

የሀገር ውስጥ ዜና

ተማሪ ሃይማኖት በዳዳን በመግደል ወንጀል ምርመራ ሲደረግበት የነበረው ደግነት ወርቁና 2ኛ ተከሳሽ ምህረቱ ሚጣ ላይ ክስ ተመሰረተ

By Tibebu Kebede

September 14, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2013(ኤፍ.ቢ.ሲ) ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በቤተ ሙከራ ክፍል ውስጥ ተማሪ ሃይማኖት በዳዳን በመግደል የወንጀል ምርመራ ሲደረግበት የነበረው ደግነት ወርቁ በውንብድና ወንጀል እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽ ምህረቱ ሚጣ ላይ ደግሞ በከባድ የመሸሸግ ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል።

ክሱ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የከባድ የውንብድና ወንጀል ችሎት የተመሰረተ ሲሆን፥ በተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መዝገቡ ታይቷል።