አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2013(ኤፍ.ቢ.ሲ) ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በቤተ ሙከራ ክፍል ውስጥ ተማሪ ሃይማኖት በዳዳን በመግደል የወንጀል ምርመራ ሲደረግበት የነበረው ደግነት ወርቁ በውንብድና ወንጀል እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽ ምህረቱ ሚጣ ላይ ደግሞ በከባድ የመሸሸግ ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል።
ክሱ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የከባድ የውንብድና ወንጀል ችሎት የተመሰረተ ሲሆን፥ በተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መዝገቡ ታይቷል።