የሀገር ውስጥ ዜና

የኮሮና ቫይረስ የመከላከል ስራን ለማጠናከርና የምርመራ አቅማቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን የጋምቤላና የሐረሪ ክልሎች አስታወቁ

By Tibebu Kebede

September 15, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮና ቫይረስ የመከላከል ስራን ለማጠናከር እና የምርመራ አቅማቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን የጋምቤላ እና የሐረሪ ክልሎች አስታወቁ።

ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የጋምቤላ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኡሙድ ኡጁሉ እና የሐረሪ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኢርዲን በድሪ፥ የኮቪድ 19 ስርጭት እየጨመረ በመሆኑ የጥንቃቄ ስራዎች ላይ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል።