አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያን በተለያዩ ሀገራት የሚወክሉ አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ከኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር ተወያዩ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ዋነኛ ተልዕኮዎች ከሆኑት ለኢትዮጵያ ወዳጅ የማብዛት፣ ገፅታ የመገንባት፣የውጭ ኢንቨስትመንት የመሳብ፣ ለኢትዮጵያ ምርቶች ገበያ የመፈለግና የዜጎችን መብት ከማስከበር በተጨማሪ ጠቃሚ ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር እንዲገባ ማመቻቸት ነው ሲሉ አስፍረዋል፡፡