የሀገር ውስጥ ዜና

አጥፊዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ለህግ እንዲቀርቡ ይደረጋል- የአማራ ክልል መንግስት

By Tibebu Kebede

December 21, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ መስጊዶች እና ቤተክርስቲያን መቃጠላቸውን ተከትሎ የክልሉ መንግስት አጥፊዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ለህግ እንደሚያቀርብ ገለፀ።

በትናንትናው እለት በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ መስጊዶች እና ቤተክርስቲያን ላይ የደረሰውን ጉዳት አስመልክቶ የክልሉ መንግስት በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቷል።