አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ መስጊዶች እና ቤተክርስቲያን መቃጠላቸውን ተከትሎ የክልሉ መንግስት አጥፊዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ለህግ እንደሚያቀርብ ገለፀ።
በትናንትናው እለት በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ መስጊዶች እና ቤተክርስቲያን ላይ የደረሰውን ጉዳት አስመልክቶ የክልሉ መንግስት በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቷል።