አዲስ አበባ ፣ መስከረም 7 ፣2013 ( ኤፍ.ቢ.ሲ)) በተያዘው የ2013 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሁለት ወራት በአገር አቀፍ ደረጃ ከ272 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር ላይ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ገቢ መሰብሰቡ ተገለጸ።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም ÷ዜጎች ለሕዳሴው ግድብ በተለያዩ ጊዜያት ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።