የሀገር ውስጥ ዜና

የምግብ ደህንነትን እና የግብርና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ የገጠር ልማትን እያስፋፋች ነው- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ

By Tibebu Kebede

September 18, 2020

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 8 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ኢትዮጵያ የምግብ ደህንነትን እና የግብርና ምርታማነትን ለማረጋገጥ የገጠር ልማትን እያስፋፋች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ገለፁ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ በቪዲዮ ኮንፈረንስ በተካሄደው የአዳጊ ሀገራት ቡድን ዓመታዊ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል።