የሀገር ውስጥ ዜና

የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በወራቤ ከተማ ከህዝቡ ተወካዮች ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

December 22, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 12፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ የተለያዩ የፌደራል እና የስልጤ ዞን ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ከዞኑ ነዋሪዎች ጋር በወራቤ ከተማ ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም በዞኑ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር እና የመሰረ ልማት ችግሮችን መፍታት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ መክረዋል።