የአማራ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሞጣ ከተማ በእስልምና እና ኦርቶዶክስ እምነት ተቋማት ላይ የደረሰውን ጥቃት አወገዘ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 12፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአማራ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሞጣ ከተማ በእስልምና እና ኦርቶዶክስ እምነት ተቋማት ላይ የደረሰውን ጥቃት በጥብቅ እንደሚያወግዝ አስታውቋል።
የክልሉ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ፥ አርብ ዕለት በሞጣ ከተማ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንና እና በእስልምና እምነት ተቋማት ላይ የደረሰው ጥቃት እምነት ያለው ሰው የሚፈፅመው ድርጊት አለመሆኑን ገልጿል።