አዲስ አበባ ፣ መስከረም 13 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅታዊ፣ ሀገራዊና ከተማ አቀፍ ጉዳዮች ላይ ከአዲስ አበባ ከአስሩም ክፍለ ከተሞች ከተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያዩ።
በውይይቱ ላይ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ ፣የአዲስ አበባ ብልፅግና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ እንዲሁም የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡