አዲስ አበባ ፣ መስከረም 14 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ግንባታ ላይ ለተሳተፉ አካላት የምስጋና የእራት ግብዣ አድርገዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የጀመራቸውን ስራዎች በሰዓቱ እንደሚጨርስ ማሳያ የሆነው የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ሙሉ ጊዜያቸውን ሰጥተው ለመሩ ፣ ላስተባበሩ እንዲሁም የግንባታው ሂደት ላይ ለተሳተፉ አካላት ነው የምስጋና የእራት ግብዣ የተደረገው።