የሀገር ውስጥ ዜና

የኢሬቻ በዓል ታዳሚዎች ለኮቪድ 19 ወረርሺኝ ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል – ዶክተር ሊያ ታደሰ

By Feven Bishaw

October 01, 2020

አዲስ አበባ ፣መስከረም 21 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የኢሬቻ በዓል ታዳሚዎች ለኮቪድ- 19 ወረርሺኝ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በጥንቃቄ ማክበር እንዳለባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አሳሰቡ።

ሚኒስትሯ ዛሬ በሰጡት መግለጫ የኢሬቻ በዓል በመሰባሰብ የሚከበር ማኅበራዊ ግንኙነቶችንና ትስስሮች የሚጠናከሩበት ታላቅ በዓል ነው ብለዋል።