አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ ሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩና ለችግር የተጋለጡ ዜጎች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር መስራቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ሚኒስቴሩ በኢትዮጵያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ በመጀመሪያው ዙር በተደረገ የማስመለስ ስራ በሳኡዲ አረቢያ ይኖሩ የነበሩና ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ 3 ሺህ 500 ኢትዮጵያዊያን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን ገልጿል፡፡