አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ዋና ጸሃፊ ከቬራ ሶንግዌ ጋር በመሆን የኮይሻ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ፡፡
ሚኒስትሩ ከተባበሩት መንግስታት ድርጀት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ስር ዋና ጸሃፊ ከቬራ ሶንግዌ ጋር ኦሞ ወንዝ ላይ እየተገነባ የሚገኘውን የጊቤ 4 ወይም ኮይሻ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብ ግንባታን እንዲሁም ሃይል በማመንጨት ላይ የሚገኘውን የጊቤ 3 የሃይል ማመንጫን ጎብኝተዋል፡፡