አዲስ አበባ ፣ መስከረም 26 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመዲናዋ በተያዘው አመት በተለያዩ አካባቢዎች 525 ኪሎ ሜትር ርቀት የሚሸፍኑ መንገዶች ጥገና ስራ ለማከናወን እቅድ መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
በ2013 በጀት አመት 525 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የአስፋልት፣ የድልድይ፣ የድሬኔጅ ፣ የአክሰስ መንገድ እና ሌሎች በርካታ ልዩ ልዩ የጥገና ስራዎችን ለማከናወን ማቀዱን ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡