የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ በተያዘው አመት 525 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ መንገዶች የጥገና ስራ ይከናወናል- ባለስልጣኑ

By Feven Bishaw

October 06, 2020

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 26 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመዲናዋ በተያዘው አመት በተለያዩ አካባቢዎች 525 ኪሎ ሜትር ርቀት የሚሸፍኑ መንገዶች ጥገና ስራ ለማከናወን እቅድ መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

በ2013 በጀት አመት 525 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የአስፋልት፣ የድልድይ፣ የድሬኔጅ ፣ የአክሰስ መንገድ እና ሌሎች በርካታ ልዩ ልዩ የጥገና ስራዎችን ለማከናወን ማቀዱን ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡