አዲስ አበባ ፣ መስከረም 26 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ እና የኢትዮጵያ ብሮድካሰት ባለስልጣን የሚዲያ ተቋማትን ከሳይበር ጥቃት መከላከል በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
ስምምነቱ የሚዲያ ተቋማትን ከማንኛውም የሳይበር ጥቃት በመከላከል አስተማማኝና ደህንነታቸው የተረጋገጠ የሚዲያ ተቋማት መገንባትን ያለመ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሹመቴ ግዛው ተናግረዋል፡፡