የሀገር ውስጥ ዜና

ከተማ አስተዳደሩ በተያዘው ዓመት ለታላቁ የህዳሴ ግድብ 789 ሚሊየን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ በ3 ወራት ብቻ ከ 500 ሚሊየን ብር በላይ ሰበሰበ

By Meseret Demissu

October 06, 2020

አዲስ አበባ ፣መስከረም 26 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ከዳር ለማድረስ የገቢ ማሰባሰብ ስራው በሰፊ ንቅናቄ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

የከተማዋ የታላቁ የኢትዮጵያ ህደሴ ግደብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ÷ በበጀት አመቱ ከ789 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለማሰባሰብ አቅዶ ባለፉት 3 ወራት ብቻ ከ500 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰብ መቻሉን ለፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖሬት አስታውቋል።