አዲስ አበባ ፣መስከረም 26 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ከዳር ለማድረስ የገቢ ማሰባሰብ ስራው በሰፊ ንቅናቄ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
የከተማዋ የታላቁ የኢትዮጵያ ህደሴ ግደብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ÷ በበጀት አመቱ ከ789 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለማሰባሰብ አቅዶ ባለፉት 3 ወራት ብቻ ከ500 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰብ መቻሉን ለፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖሬት አስታውቋል።