አዲስ አበባ ፣መስከረም 26 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከአፍሪካ የደህንነት ጥናት ተቋም ዳይሬክተር ዶክተር ፎንቴህ አኩም እና የተቋሙ የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ዳይሬክተርና የአፍሪካ ህብረት ተወካይ ከሆኑት ዶክተር ሮባ ሻራሞ ጋር ተወያይተዋል።
አምባሳደር ሬድዋን በዚህ ወቅት አፍሪካዊያን በተለያዩ መስኮች ላይ በትብብር መስራትን አጠናክረው መቀጠል እንዲችሉ ከማድረግ አንጻር ተቋሙ ሰፊ እንቀስቃሴ እንደሚጠበቅበት ገልጸዋል።