የሀገር ውስጥ ዜና

በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ በግለሰቦች መካከል በተፈጠረ ግጭት የ12 ዜጎች ህይወት አለፈ

By Abrham Fekede

October 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 2፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ድኋንዝ ባጉና ቀበሌ በግለሰቦች መካከል በተፈጠረ ግጭት የ12 ንጹሃን ዜጎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሰላም ግንባታና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጋሹ ዱጋዝ ግጭቱ ትናንት ከሌሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ መነሳቱን ነው የገለጹት።