የሀገር ውስጥ ዜና

የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ባህሪያት ከሥርዓተ ምግብ ጋር ያለውን መስተጋብር የተመለከተ ጥናት ተጀመረ

By Meseret Demissu

October 21, 2020

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 11 ፣2013 (ኤፍ.ቢ. ሲ) የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት የኮቪድ19 ወረርሽኝ ባህሪያት ከሥርዓተ ምግብ ጋር ያለውን መስተጋብር አስመልክቶ ለአንድ አመት የሚቆይ ጥናት በይፋ አስጀመረ።

በዚህም በህክምና ማገገሚያ ውስጥ ቆይታ በነበራቸው ታካሚዎች ላይ ክትትል እና ጥናት በማድረግ መፍትሄዎችን ለማስቀመጥ የሚያስችል ለአንድ አመት የሚቆይ ጥናት በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት፣ ከጤና ሚኒስቴር እና ከልዩ ልዩ የልማት አጋሮች ጋር በመተባበር ለማከናወን ታቅዶ ሥራው በይፋ ተጀምሯል።