አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 12 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአማራ ክልል የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ከመድረሳቸው በፊት ቀድሞ መከላከል የሚያስችል ከ220 ሚሊየን ብር በላይ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።
ከነገ ጀምሮ ወደ ሥራ የሚገባው ይህ ፕሮጀክት በክልሉ በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች የማይበገር ማኅበረሰብ ለመፍጠር የሚደረገውን ሥራ የሚያግዝ መሆኑን የአማራ ክልል አደጋ መከላከል፣ ምግብ ዋስትናና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘላለም ልጃለም ተናግረዋል።